1
የወያኔ የህልውና መድህን አክራሪና የመገንጠል
ዓላማ የተጠናወታቸው ቡድኖች ናቸው
የኢትዮጲያ ህዝብ በወያኔ ጨካኝ አገዛዝ እየተሰቃየ በመሆኑ በተለያያ ጊዜያት
ተቃውሞውን በተለያየ የአገራችን ክፍል ገልጿል። በዚህም ብዙ የንጹሃን ደም ፈሷል።
በቅርብ ጊዜ በኦሮሚያ የአገራችን ክፍል እየተካሄደ ያለው የህዝብ እምቢተኝነት የወያኔ
አገዛዝ ካጋጠመው ፈተና ሁሉ ከፍተኛው ነው። ይህን የድል ተስፋ የታየበትና፣ ብዙ
ንጹህ ዜጎች መስዋዕት የሆኑለትን እምቢተኝነት ለማፈን ወያኔወች ብዙ ታንክና የአጋዚ
ጦር ከማሰለፍ የበለጠ ተቃዋሚወችን በዘርና በቋንቋ መከፋፈልን ይመርጣሉ። ለወያኔወች
የህልውናቸው መድህን አክራሪና የመገንጠል ዓላማ የተጠናወታቸው ቡድኖችና ግለሰቦች
ናቸው። ኢትዮጲያዊ ከኢትዮጲያ አንድነትና ሉዓላዊነት በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ምንም
ነገር የለም።
በኦሮሚያ የሚካሄደውን የህዝብ እምቢተኝነት ለምን ሌላው የአገሪቱ ህዝብ ለመቀላቀል
ተቸገረ ወይም ዘገየ የሚለው የወቅቱ የመወያያ ርዕስ ሆኗል። ደርግ የፈጠረብንን ጊዚያዊ
የአምባገነን በሽታ፣ ወያኔ በቀላሉ በማይነቀልና ለአገር አንድነት አስጊ በሆነ የዘረኝነት
በሽታ ተክቶታል። በአሁኑ ጊዜ የሚደረገው ትግል አምባገነኑንና ጎሰኛውን የወያኔ አገዛዝ
ከስልጣን አውርዶ፣አንድነቷና ሉአላዊነቷ በተጠበቀች ኢትዮጲያችን የህግ የበላይነት
የሰፈነበት ዲሞክራሲያዊ መንግስት መመስረት ነው።
ኢትዮጲያዊ ለአገሩ ሉዓላዊነትና አንድነት ቅድሚያ እንደሚሰጥ የተረዳው ወያኔ፣
ተቃዋሚወችን የመምቻው ዋና መሳሪያ መከፋፈልና፣ የመገንጠል አቋም የሚያራምዱ
ወገኖችን አሰልጥኖ ማሰለፍ ነው። ጎሽ ለልጇ ስትል ተወጋች እንደሚባለው፣
ኢትዮጲያዊያን ለአገራቸው አንድነት ሲሉ ብዙ ጥቃትና ግፍን ተሽክመው ቆይተዋል።
ከዚህ አንጻር የምናየው ሰሞኑን እየተደረገ ያለውን ትግል የዘርኝነት ተልዕኮ ያላቸው
ግለሰቦች በመጥለፍ “የኦሮሞ ሕዝብ የአገር ባለቤትነት” የሚደረግ ትግል
ነው፣ “ኦሮሚያ የኦሮሞ ናት” በማለት ብዙውን የኢትዮጲያ ህዝብ ትግሉን
እንዳይቀላቀልና አገሩን ከወያኔ የግፍ አገዛዝ ነጻ እንዳያወጣ መሰናክል እየሆኑበት ነው።
እነዚህ ወያኔ ካሳያቸው የጎሳ መስመር ዉጭ ማሰብ የማይችሉ ጠባብና ዘረኛ አካሄድ የያዙ
ወገኖች የሚከፈለውን መስዋእትነት መልካም ዉጤት እንዳይኖረው እያደረጉ ነው።
ትግሉን ሊቀላቀል የሚገባውን ህዝብ ገፍተው እያራቁት ነው።
ይህን የኦሮሞ ወጣቶች በኢትዮጲያ ለፍትህና ለህግ የበላይነት የሚደረግ ትግል አቅጣጫ
ለማስቀየርና፣ በህዝብ ዘንድ ጥላቻን ለመዝራት የሚጠቀሙባቸውን ግለሰቦች ምንነታቸውን
ማወቅ አስፈላጊ ነው። ግለሰቦቹ ከተለያየ አቅጣጫ አስተያየት ቢሰጣቸውም ለትግሉ
መሰናክል መሆናችውን ሊያቆሙ ባለመቻላቸው ጥፋታቸውን በግልጽ ማሳየት አስፈላጊ
ሆኗል።እነዚህም ግለስቦች እየፈጸሙ ያለውን ስህተት ቆም ብለው ማሰብና አሁንም
አቋማቸውን መመርመር ይገባቸዋል።
2
የኦሮሞን ህዝብ ከሌላው የኢትዮጲያ ህዝብ፣ ሙስሊሙን ኦሮሞ፣ ከክርስቲያኑ ኦሮሞ፣
ወያኔ በነደፈው ዘዴ፣ ለማጣላት የሚቀሰቅሱ የወቅቱ የዘር ጥላቻ ማዕከል የሆኑ ግለሰቦች
ከዚህ አጥፊ ተግባራቸው ሊታቀቡ ይገባል። ከነዚህ ግለሰቦች ተግባር ከወንጀለኞቹ
ወያኔወች በስተቀር የሚጠቀም የለም። ይህን በማድረግ ቅድሚያ ከሚጠራው አንዱ
ወጣት ከአገሩ የወጣው ገና የአስረኛ ክፍል ትምህርቱን እንደጨረሰ ሲሆን፣ በኦነግ
ተዋጊወች ተኮትኩቸ አድጊያለሁ፣ ቁቤ ያስተማሩኝ የኦነግ ተዋጊወች ናቸው፣ ከማለቱ
በስተቀር ስለኢትዮጲያና የኢትዮጲያ ህዝብ አኗኗር መስተጋብርና ታሪክ ብዙም ግንዛቤ
የለውም፣ ወይንም እንደተማረ ሰው እውነቱን ለመመርመርና ለማወቅ አይፈልግም። ይህ
በዚህ በወጣትነት እድሜው ኢትዮጲያን ባልተለመደ መንገድ ለቆ የወጣ ወጣት፣
የቀደምት ኦነግ መሪወች እርግፍ አድርገው የተውትን፣ የማያዋጣና ጊዜው ያለፈበት
አቋም፣ ለምን የራምዳል?
ይህ ግለሰብ ሰሞኑን ይህን ብሏል፤
"ኦሮሚያ የኦሮሞ ነች" የሚለው መሪ ሀሳብ በአሁኑ ወቅት በትግሉ ውስጥ ያለን የኦሮሞ
ወጣቶች ያመጣነው ወቅታዊ መፈክር ሳይሆን የዛሬ አመሳ አመት ገደማ የኦሮሞ ተጋዮች
ለነፃነታቸውና ለእኩልነት ትግል ሲጀምሩ የትግሉ ዋና መሰረት በማድረግ አንግበውት
የተነሱት የሀገር በለቤትነት (mirga abbaa biyyummaa) ጥያቄ ነው።…..ይህ ማለት ኬኒያ
ወይም ኦሮሚያ ውስጥ ሌላ ሰው መኖር ዜጋ መሆን አይችልም ማለት አይደለም። በሚገባ
ይችላለ። የማይቻለው ሀገሬው ተገፍቶ የሀር ባለቤትነት መብቱን ተነጥቆ ሌላው
ሊንደላቀቅበት ማሰቡ ነው። እናም ኦሮሚያ የኦሮሞ ነች የሚለውን መፈክር ልናፍርበት
ሳይሆን በደማችን እውን ለማድረግ እየታገልንለት ያለ ህያው አላማችን ነው።”
ቀድም ባለ ጊዜ ግለሰቡ ይህን ብሎ ነበር፤
“እኔ ባለሁበት ዘጠና ዘጠኝ በመቶ ሙስሊም ነው ስለዚህ ማንም ሰው ደፍሮ ቀና
አይልም፣ በሜጫ ነው አንገቱን የምንለው”
እንደዚሁም ቀደም ብሎ ለወያኔ መንግስት ዲፕሎማት የነበረ ግለሰብ አሁን የዚህን ሰው
አላማ “ለአገር ባለቤትነነት የሚደረግ ትግል ነው” በማለት በማራገብ ላይ ነው።
እነዚህን የመሳሰሉ ግለሰቦች የወያኔን የግፍ አገዛዝ ለመስወገድ የሚታገለውን ህዝብ
በኦሮሚያ አካባቢ የሚደረገውን ትግል በጥርጣሬ እንዲያየውና የተከፈለው የህይወት
መስዋትነት ለድል እንዳይበቃ እያደረጉ ነው።
ተረግጦ እየተገዛ ያለው የኢትዮጲያ ህዝብ የነዚህ አይነት አፍራሽና ከፋፋይ ተልዕኮ
ያላቸውን ግለስቦች በአግባቡ ለይቶ በማወቅ ጊዜው ሳይዘገይ ሊመክራቸው
ሊያስመክራቸውና ሊመልሳቸው ይገባል። ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርን፣ ከመገንጠል ይልቅ
አንድነትን ማስተማር አለባቸው። በዚህ መንገድ ስህተታቸውን አስተካክለው ከሌላው
የኢትዮጲያ ህዝብ ጋር በመተባበር ትግሉን ለድል ለማብቃት አስተዋጾ ማድረግ
አለባቸው። ትግሉን በአገራዊ ጉዳይ ዙሪያ በማስተባበርና፣ በሰለጠነ መንገድ
በመወያየት፣ የጋር ስልት በመንደፍ፣ በአንድ ሆኖ ወያኔን መታገልና ከስልጣን ማውረድ
3
ይገባል። በወያኔ ኢሰብአዊ አገዛዝ መከራውን የሚያየው የኢትዮጲያ ህዝብ ከሁሉም
ጎሳ፣ ከሁሉም አካባቢ፣ ከሁሉም ሃይማኖት ነው። ከግፍ ፈጻሚወቹ በስተቀር በወያኔ
የልተበደለ ኢትዮጲያዊ የለም።
ደረቱን ለአጋዚ ጥይት ሰጥቶ መስዋዕትነት እየከፈለ ያለው ኢትዮጲያዊ አንዱን ዘረኛ
አውርዶ በሌላ ዘረኛ ለመተካት ወይንም አገር ለማፍረስ አይደለም። ስለዚህ እነዚህን
ከፋፋይ የሆኑ፣ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ የወያኔ ተልዕኮ ያላቸው፣ ዘርን ከዘር፣
ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጣሉ፣ ግለሰቦች የወያኔን የስልጣን እድሜ እንዲያራዝሙ
ሊፈቀድላቸው አይገባም። እንደነዚህ አይነት ወደፊት ከማሰብ ይልቅ ወደኋላ ማሰብ
የሚቀናቸው፣ ከአንድነታችን ይልቅ ስለልዩነታችን ብቻ መናገር ስራቸው የሆነ፣ ግለሰቦች
ለዘመናት አብሮ የኖረውን፣ በደም የተሳሰረውን፣ የኢትዮጲያ ህዝብ ለመከፋፈልና፣
የአንድነት ታሪኩን ለማራከስ የሚያደርጉት ስራ አደገኛ በመሆኑ ሁሉም ኢትዮጲያዊ
ሊቃወመውና ይገባል። የኢትዮጲያ ህዝብ በዘር በሃይማኖት ሳይከፋፈል በችግሩ ላይ
በእውነትና፣ መልካም ዉጤት ለማምጣት፣ በመወያየትና፣ ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ
የጋራ መፍትሄ በመፈለግ፣ የወያኔን ጨካኝ አገዛዝ ለመጣል የሚያደረገውን ትግል
አጠናክሮና አስተባብሮ ሊቀጥል ይገባል። ሁሉም ኢትዮጲያዊ በጋራ በመወያየት
ለትግሉ ግልጽ ስልትና አላማ በመንደፍ በጋራ መስራት የወቅቱ ተቀዳሚ ጥያቄ ነው።
የወያኔን የጭካኔ አገዛዝ ለማስወገድና፣ የተሻለ አስተዳደር ለኢትዮጲያ ህዝብ ለማምጣት፣
ምንጊዜም ቢሆን ከአንድነት ውጭ አማራጭ የለንም። አንድነት ኃይል ነው።
ኢትዮጲያ በአንድነቷ ለዘላለም ትኑር!
አበራ ቱጂ
አዲስ አበባ
ኢትዮሚድያ - Ethiomedia.com
February 22, 2016
No comments:
Post a Comment