Thursday, September 1, 2016

በብዙ የጎጃምና የጎንደር አካባቢዎች መንግሥት ፈርሷል፤ የጎበዝ አለቆች ክፍተቱን እየሞሉ ነው ክፍል አንድ፤ #AmharaResistance; • ባሕር ዳር፣ መራዊና ዳንግላ ከተሞች በጪስ ታፍነው ተኩስ ሲናጡ ውለዋል • ‹‹በአዴት ከተወለዱ በጤና እያለ አንድስ እንኳ እቤት የዋለ የለም›› የአዴት ሪፖርታዥ • ከወረታ ከተማ አቅራቢያ ጉማራ ላይ በገበሬውና በወያኔ መከላከያ መካከል ከባድ ጦርነት ሲደር ግ አድሯል • ቋሪት፣ አገው ምድር፣ ጋይንት፣ በለሳ፣ አብዛኛው የደባርቅና የጃናሞራ አካባቢዎች ከመንግሥት ቁጥጥር ውጭ ናቸው • በአንዳቤትና በፋርጣ የጎበዝ አለቆች አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል ባሕር ዳር፤ በባሕር ዳር ከተማ በሕዝብ የተጠረውን የቤት ውስጥ አድማ ለማደናቀፍ በሞከሩ የወ ያኔ አባላትና ቅጥረኛ ባንዳዎች ንብረት ላይ ዐማራው እርምጃ እየወሰደ ነው። የዐማራው ሕዝብ ቆራጥነቱን በተግባር ያሳየበት ከዛሬ የበለጠ ቀን አልነበረም። ጠዋትአካባቢ አድማውን ችላ በማለት ሥራ የጀመረ አንድ የከተማ አውቶቡስ ሾፌር መኪናውን ሰ ባብረው ልጁን እንዲማር መጠነኛ አካላዊ ጉዳት ደርሶበት አሰናበቱት፡፡ ሥራ የጀመረው የንግድ ባንክም ሕንጻ መስኮቶች ተሰባብረዋል፡፡ በሕዝብ አስቀድመው የተለዩየሕወሓት አባላት እና የዐማራ ቅጥረኛ ባንዳ ሰዎች ስም ዝርዝር አስ ቀድሞ የተሰራ ሲሆን ተራ በተራ ሲቃጠል ውሏል፡፡ ባሕር ዳር አሁን ከዝናቡ ጋር በጭስ ታፍናለች። ከቦታው አስተያየቱን እንዲሰጠን የጠየቅነው የከተማዋ ነዋሪ ‹‹የጥይት ሩምታው ይሰማሃል?የቤት ጣራ ላይ ሆኜ ነው የማወራህ አንድ ሁለት… ወደ ዘጠኝ ቤት ሲቃጠል ይታየኛል እኛ ሰፈር እንኳ የአምቡላንስና የጥይት ድምጽ እየረበሸኝ ነው›› ሲል የነበረበትን ሁኔታ ገልጦልናል፡፡ ቀበሌ 08 የሚባለው ሰፈር በርካታ ቤቶች የተቃጠሉበት ነው ተብሏል፡፡ በባሕር ዳር በዛሬው የዐማራ ተጋድሎ ቀበሌ 06 ሦስት ዐማሮች ተሰውተዋል፡፡ ቀበሌ 14 ኤፍራታ እሚባለው አካባቢ ደግሞ ለታጋይ ዐማሮች ውሃና ምግብ ለማቅረብ ሲሄዱ የነበ ሩ እናት ወድቀው መሰዋታቸውን ሰምተናል፡፡ በርካታ ተሸከርካሪዎች የተቃጠሉ ሲሆን ዐማራው በየሰፈሩ የጎበዝ አለቃዎችን እየመረጠ በመታገል ላይ መሆኑን ሰምተናል፡፡ ያልተዘጋ መንገድ የለም፡፡ የዐማራ ፖሊስ ሕዝብን በመጠበቅ ያደረገው ተጋድሎ የሚደነቅ መሆኑን ሰምተናል፡፡ በባሕር ዳር ዛሬ የተደረገው ተጋድሎ እጅግ የሚያኮራናከተማዋን ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ ሕ ዝቡ የተቆጣጠረበት ሁኔታ እንዳለ ሰምተናል፡፡ የባሕር ዳር ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች በግቢ የዐማራን ተጋድሎ ሲያንጸባርቁ ውለዋል፡፡ ከባሕር ዳር ከተማ 17 ኪሎ ሜትር አካባቢ ያለችው የመሸንቲ ከተማና የይባብ ኢየሱስ ቀበሌም የ ዐማራ ተጋድሎ ከዋለባቸው ቦታዎች ውስጥ ናቸው፡፡ መሸንቲ ያለው የሕወሓት አባል የድንጋይ ጠጠር ማምረቻ ፕላንትም ተቃጥሏል ተብለናል፡፡ መራዊ፤ በመራዊ ከተማ የዐማራ ሕዝብ ለተጋድሎ የወጣው በጠዋት ነበር፡፡ የሜጫዋ መራዊ ከተማ እንደ ባሕር ዳር ሁሉ በጢስ ታፍና ውላለች፡፡ ለተጋድሎ የወጣው የዐማራ ሕዝብ ከጉያው ተሸጉጠው ሲያንገላቱት የነበሩትን የሕወሓት አባላትና ቅጥረኛ ባንዳዎችሀብትና ንብረት ተለቅሞ ተቃጥሏል፡፡ የገብረ ሥላሴ ኃይለማርያም ክሊኒክና ፋርማሲ፣ የገ/ድህን ክሊኒክ፣ ፒታ ዳቦ ቤት፣ ኃይሌ ፎቅ፣ የኢትዮጵያ እህል ንግድ ድርጅት፣ ብአዴን ጽ/ቤትና በርካታ የሰላዮች መኖሪያ ቤትና ንብረት ወ ድሟል፡፡ የዐማራ ሕዝብከተማዋን ይህ ሪፖርት እስከተሠራበት ጊዜ ድረስ ተቆጣጥሯት ይገኝ እንደነበር ለማ ወቅ ችለናል፡፡ አዴት፤ የይልማና ዴንሳዋ አዴት ከተማ በዐማራ ተጋድሎ ስትናጥ ውላለች፡፡ ከአዴት ከተማ የሚገኘው ሪፖርተራችን የላከልን መረጃ እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡ የአዴት ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ ወያኔን ሲቃወም ዋለ፡፡ በአዴት ከተወለዱ በጤና እያለ አንድስ እንኳእቤት የዋለ የለም፡፡ ከወጣት እስከ ሽማግሌ፣ ሴትና ወንድ፣ እስላምና ክርስቲያን ሁሉ በቁጣ ገንፍሎ ወጥቷል፡፡ ሰልፉን የሰሙ የይልማና ዴንሳ አርሶ አደሮችም ከወንዳጣ ድረስ እየመጡ በወኔ ተጋድሎውን ተቀ ላቅለው ውለዋል፡፡ ‹‹ወያኔ ሕወሓት ሌባ ነው፤ ቅጥረኛው ብአዴን አይወክለንም፤ ድንበራችን ተከዜ ነው፤ ወልቃይት ዐማራ ነው፤ በዐማራ ላይ የሚደርሰው ጭቆና ይቁም፤ የሃይማኖት ጣልቃ ገብነት ይቁም፤ …›› እ ና ሌሎችም መፈክሮች ሲሰሙ ውለዋል፡፡ የዐማራው ሕዝብ ወደባሕር ዳር በኩል 2 ኪሎ ሜትር መንገድ በመጓዝ አቦላ ተራራ አካባቢ ያለ ውን መንገድ መዝጋት ቅድሚያ የሠጠው መርሃ ግብር ነበር፤ ይህም የወያኔን አልሞ ተኳሾች እን ዳይመጡ መንገዱን ማበላሸት ሲሆን ይህን የሰሙት የባሕር ዳር አናብስት ወጣቶች ሰባታሚትአካባ ቢ መንገዱን ጠርቅመው በመዝጋት የአዴት ዐማሮችን ተባብረዋል፡፡ ሰልፈኞች ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩ ወጣቶችን ሰብረው በመግባት አስፈትተዋል፤ የአስተዳደር ቢሮው ተሰባብሯል፡፡የገንዘብና ኢኮኖሚ ጽ/ቤት ኮምፕዩተሮች በእሳት ጋይተዋል፡፡ አካለመንግሥቱ የሚባለው የወያኔ ቅጠረኛ ዐማሮችን ሲሰልልና ሲያሰቃይ የሰነበተ ሲሆን የሕንጻ መሣሪያ መደብሩ ወድሞበታል፡፡ ክሊኒክና ፋርማሲ በመክፈት የአዴት ዐማራን ጊዜው ባለፈበት መድኃኒት ሲበዘብዙና ሲሰልሉ የነ በሩት የገ/እግዚአብሔር ቤተሰቦች ከሳምንታት ቀደም ብለው ከአዴት ቢወጡም ንብረታቸውና መ ኖሪያ ቤታቸው በእሳት ከመጋየት አልዳነም፡፡ የገ/እግዚአብሔር ልጅየሆነው አቶ አማኑኤል ዐማሮችን በሽጉጥ ሲያስፈራራ የሰነበተ ሲሆን ዛሬ ተ ፈልጎ የገባበት ሳይታወቅ ቀርቷል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ የወያኔ ቀኝ እጅ የሆኑት የሃይማኖት አባቶች ሰልፉን ለመገላገል ቢገቡም እናን ተን አንሰማም ብሎ አሳፍሮ መልሷቸዋል፡፡ ይልማና ዴንሳበህዝብ ቁጥጥር ስር ውላለች፡፡ ለዘጋቢያችን ምስጋና ይድረሰው፡፡ ዳንግላ፤ የአገው ምድሯ ዳንግላ ከተማ የዐማራን ተጋድሎ የተቀላቀለችው ትናንት ነበር፡፡ ትናንት ነሃሴ 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ከጠዋቱ 1ጀምሮ የዳንግላ አገው ዐማራ ሕዝብ ለተጋድሎ ወጣ፡ የዐማራውን ጥያቄዎች አንግቦ ወደ ወኅኒ ቤቱ አቅጣጫ ሲሄድመዘጋጃ ቤት አካባቢ ሲደርስ የወያ ኔ አባል የሆነው የመዘጋጃ ቤት ሠራተኛ አቶ ሀብተወልድ ወደ ሕዝብ በመተኮስ ሁለት ሰዎችን አቆሰለ፡፡ሕዝብ ተቆጣና የአቶ ሀብተወልድን ቤት ሙሉ በሙሉ አቃጠለው፡፡ ወደ መሃል ከተማ ሲመጣ አንድ ቅጥረኛ የሆነ ያረጋል የሚባል ፖሊስ የዳሸን ቢራ ማስታወቂያን ከሚቀዱት የአገው ዐማራ ወጣቶች ላይ ጥይት አርከፈከፈ፡፡ ፖሊሱ የቤቱን አጥር ጉድብ ይዞ ሁለት ሰዎችን ገደለ፡፡ ከሕዝብ ጋር በሚያደርገው ትንቅንቅ ጥይትጨረሰ፡፡ ሕዝቡ ሊይዘው ሲል ጎረቤቱ አንድ ካዝና ጥይት ሲሰጠው አናብስቶቹ አዩት፡፡ ባንዳው ጎረቤቱ ተጨፍጭፎ ተገደለ፡፡ፖሊሱ ቢያመልጥም ቤቱ ከመቃጠል አላመለጠም፡፡ ይህ ሙሰኛ ፖሊስ መኖሪያ ቤት ውስጥ 50 ኩንታል ስኳርና 20 ጀሪካ ዘይትተደብቆ ተገኘ፡፡ ሁሉም ንብረት አብሮ እንዲወድም ተደረገ፡፡ መኪናም ነበረችው፤ ወደመች፡፡ ዳንግላዎች ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ ነሃሴ 23 ቀን ጠባ፡፡ ዳግም ለተጋድሎ ተሰለፉ፡፡ ከዚያም ዳንግላ ከተማ ከክረምት ጉም እኩል የእሳት ጭስ አፈናት፡፡ የህወሓት አባላትና የቅጥረኛ ባለሥልጣናት ቤት ሙሉ በሙሉ ወደመ፡፡ ከተማዋም በሕዝብ ቁጥጥር ሥር ሆነች፡፡ የከንቲቫው (አቶ ሙላት እሸቴ) በሙስና የተከማቹ ሦስት ቤቶች፣ የጥቃቅን ኃላፊው አቶ ያለው ዘ ለቀ፣ የብአዴን ኃላፊው አቶ ዳዊት ብርሃኑ፣ የማዘጋጃ ኃላፊው አቶ መንግሥቴ ቢተው፣ የትራፊ ክ ፖሊሱ አቶ አይተነው፣ የደኅንነቱ አቶ ይመኑ፣ እና ሌሎችም ዛሬ ወደአመድነት ከተለወጡ በ ቶች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ የአጋዚና የፌደራል ፖሊስ አባላት ከተማዋን ቢወሯትም ሕዝብን ግን እስካሁን ማሸነፍ አልተቻለ ም፡፡ ክፍል ሁለት፤ #AmharaResistance; ዱርቤቴ፤ የዱርቤቴ እና የሰሜን አቸፈር ወረዳዋ ይስማላ ከተማዎች በዐማራ ተጋድሎ ሲናጡ ው ለዋል፡፡ የአቸፈር ገበሬዎች የይስማላ ከተማን መቆጣጠራቸው የታወቀ ሲሆን በዱርቤቴ ደግሞ የጎበዝ አለ ቃዎች ምርጫ ተካሒዷል፡ዝርዝር መረጃዎችን በኔትወርክምክንያት ማቅረብ አልቻልንም፡፡ እንጅባራ፤ በእንጅራባራ ከተማ ትናንት ነሃሴ 22 ቀን 2008 ዓ.ም. በተካሔደው የዐማራ ተጋድሎ ከመቶ ሺህ በላይ ሕዝብ ወጥቷል፡፡ የሕዝቡን ብዛት ሲገልጹ በባሕር ዳር፣ በጃግኒና በአዲስ አበባ መውጫ መንገዶች እስከ ሦስት ኪሎ ሜትር ድረስ የሚረዝምየሰው ጎርፍ ነበር ብለዋል መረጃዎቻችን፡፡ ወልቃት ዐማራ ነው፤ የታሠሩ ኮሚቴዎቻችን ይፈቱ፤ ዐማራነት ወንጀል አይደለም፤ የሚሉና ሌ ሎችም መፈክሮች ተሰምተል፡፡ በእንጅባራ በዞኑ ጸጥታ ዘርፍ የሚሠራ አንድ ታፈረ የሚባል አገው ዐማሮችን በማሰቃየት የታወ ቀ ቅጥረኛ በሕግ አምላክ እየተባለ አንድ ሰው ገደለ፡፡ ከዚያ የትግሬ አጋዚ ሠራዊት ደርሶ ሌሎች 5 አገው ዐማሮችን የገደለ ሲሆን 19 ሰዎችን ደግሞ አ ቁስሏል፡፡ ሕዝቡበንዴት እና በደም ፍላት አቶ ታፈረ የተባለውን ባንዳ ሊገድል ቢሞክርም በማምለጡ ልጁ ተገድሏል፡፡ሕዝብ በንዴት ወደ ቤት ሳይገባ በውጭ አድሯል፡፡ የእንጅባራ የዐማራ ተጋድሎ ዛሬም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን በርካታ የሕወሓት አባላትና የቅጥር ባንዳ ዎች መኖሪያ ቤቶችና ንብረቶች ተቃጥለዋል፡፡ እንጅባራም በጭስ ታፍነው ከዋሉ ከተሞች አንደኛ ሆናለች፡፡ የአገዚ ጦር ዛሬ ሌሎች 6 ወንድሞቻችን በሞት ነጥቆናል፡፡ የአባቶቻችን ሰንደቅ ዓላማ ዛሬም እየተውለበለበ ሲሆን የእንጅባራ ከተማ አሁንም በሕዝብ ቁጥጥር ሥር ነው፡፡በርካታ መኪናዎች እየተቃጠሉ ነው፡፡ የተጋድሎው መቀጠል አለመቀጠል በተመከተ ለአንድ የእንጅባራ ነዋሪ ላቀረብንላቸው ጥያቄ ‹‹ገ ና ገና ገና ይቀጥላል!›› ሲሉ በሙሉ ልብና በእርግጠኛነት ተናግረዋል፡፡ እኚሁ አስተያየት ሰጪ እንደሚሉት ‹‹የዐማራ ጥያቄ ሳይመልስ መቼም ቢሆን እኛ አናቆምም፤ መንግሥቱን አፍርሰነዋል፤ ቀጣይ ሥራችንም የጎበዝ አለቆችን መምረጥ ነው፤ ወቅቱ የአዝመራ ጊዜ ቢሆንም ገበሬው ከነጻነት በኃላ ይደርሳል እያለ እየተቀላቀለን ነው›› ሲሉ አክለው ገልጸዋል፡፡ ስማዳ፤ የስማዳዋ ወገዳ ከተማ ዐማሮች ዛሬ በጠዋት ነበር ተጋድሏቸውን የጀመሩት፡፡ ዛሬ ሦስት አካበቢ የተጀመረው የዐማራ ተጋድሎ የዐማራውን ሕዝብ ጥያቄ ሲያስተጋባ ከዋለ በኋላ የአባቶቻችን ሰንደቅ ዓላማ በክብር ተውለብልባለች፡፡ በወረዳው የወያኔ ቅጥረኛየሆነ አንድ ፖሊስ ሦስት ያክል ሰዎችን ገድሎ ከዐሥር በላይ ደግሞ ማቁ ሰሉን ከቦታው አረጋግጠናል፡፡ ዛሬ በስማዳ የተሰው ዐማሮች ጠቅላላ አምስት ደርሷል፡፡ የአስተዳደር ቢሮ ተሰብሮ ቅጥረኛው ኃላፊ ከከተማዋ ተሰውሯል፡፡ ማንኛውም ዓይነት እንቅስቃሴየቆመ ሲሆን በአቅራቢያ ባሉ የሙጃና የሦስቻም የገጠር ቀበሌዎችም ላይ ተጋድሎ እንደነበር ለማወቅ ችለናል፡፡ ጃግኒ/ መተከል፤ ዛሬ በጃግኒና በመተከል ባሉ ከተማዎች የዐማራ ተጋድሎ ቀጥሎ የዋለ ቢሆንም በስልክ ችግር የተሟላ መረጃ ማቅረብ አልቻልንም፡፡ አንዳቤት/ጃራ ገዶ፤ የአንዳቤት ዐማሮች ዛሬ ሳይነጋ ሌሊት ዘጠኝ ሰአት ነበር የዐማራውን ተጋድ ሎ የጀመሩት፡፡ የጃራ ገዶ ከተማ ከወልሽ ከተማ 10 ኪሎ ሜትር የምትርቅ ሲሆን በሌሊት የወጣው ዐማራ አንዳ ቤት ወረዳን ድብልቅልቅ አድርጓት ውሏል፡፡ የወልሽከተማ ነዋሪዎች ወደ ጃራ ገዶ በመሄድ የጃራ ገዶ ደግሞ ወደ ወለሽ በመምጣት አዳማ የ ሚባለው አካባቢ ተገናኝተዋል፡፡ የአንዳቤት ዐማሮች የጎበዝ አለቆችን እየመረጡ ሲሆን ቀጣይ ቀናት ወረዳው ሙሉ በሙሉ በሕዝብ ቁጥጥር ሥር ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በአንዳቤት 5 ዐማሮች በቅጥረኛ ታጣቂዎች የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ቢሆንም የሰው ሕይወት አለመጥፋቱን ሰምተናል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ የእስቴዋ መካነየሱስ ከተማ በቤት ውስጥ አድማ መመታቷን ሰምተናል፡፡ የእስቴ መካነየሱስ መንገዶች በሰውና በመኪና ድርቀት ተመተው ውለዋል፡፡ የእስቴን ጤፍ ዘርገቶ የሚይዘው የመካነየሱስ ገበያ አእዋፋት ብቻ ወረውት ውለዋል፡፡ የመካነየሱስ የቤት ውስጥ አድማ ነገም ይቀጥላል፡፡ ጋይንት/ ነፋስ መውጫ፤ ትናንት ነሃሴ 22 ቀን የተጀመረው የቤት ውስጥ አድማ በጽጥታ አካላት ጣልቃ ገብነት ደፈረሰ፡፡የጋይንት አናብስት ተቆጡ፡፡ ተኩስ ተጀመረ፡፡ አንድ ቅጥረኛ ፖሊስ ሦስት ዐማሮችን በጥይት አቆሰለ፡፡ሕዝቡ ሊገድለው ሲል አመለጠ፡፡ ቤቱ ሔዱ፡፡ ተከራይ ሆኖ አገኙት፡፡የቤቱን ሙሉ እቃ አውጥተው አስፓልት ላይ አቃጠሉት፡፡ ዐማሮች ከተማዋን ተቆጣጠሩ፡፡ የጋይንት ዐማሮች ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሎ ዋለ፡፡ በጨጭሆ በኩልና በደብረ ታቦር መምጫ መንገዶች በሚገባ ተዘግተዋል፡፡ የነፋስ መውጫ ከተማ ሙሉ በሙሉ በዐማሮች እጅ ከሆነች ሁለተኛ ቀኗን አስቆጥራለች፡፡ የጋይንት ወጣቶች በአድማው የሚበሉትን ላጡሰዎች የምግብ እና የመጠጥ እርዳታ አድርገዋል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ የታች ጋይንት ዐማሮችም ለተጋድሎ መውጣታቸውን ብንሰማም ከቦታው ያገኘነ ው መረጃ ባለመኖሩ ማካተት አልቻልንም፡፡ ደብረ ታቦር፤ የደ/ታቦር ዐማሮች የቤት ውስጥ አድማ ከመቱ ሁለተኛ ቀናቸው ነው፡፡ አንዳንድ ቅጥረኞች ሥራ ለመጀመር ትናንት እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ያን የተቃወሙት የታቦር ል ጆች በቅጥረኛ ወታደሮች ሁለት ወንድሞቻችን ተነጥቀዋል፡፡ በደብረ ታቦር 94 ቅጥረኛ ሰላዮች የተለዩ ሲሆን በሚቀጥሉት ቀናት ዐማራው ሕዝብ እርምጃ እንደ ሚወስድ ይጠበቃል ሲሉአስተያየት የሠጡን ሰዎች ገልጸዋል፡፡ የታቦር ዐማሮች የፌደራል ፖሊሶችን መሣሪያም መንጠቃቸውን ሰምተናል፡፡ በጎበዝ አለቆችምመደራጀት ተጀምሯል፡፡ ደብረ ታቦር ግማሽ ነጻነት ላይ ያለች ከተማ ናት፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ የጋሳይና የክምር ድንጋይ ዐማሮች የካቢኔ አመራሮችን በሙሉ ማስወገዳቸውም ተገልጧል፡፡ጋሳይና ክምር ድንጋይ መንገዶች ዝግ ናቸው፡፡ ወረታ/ ጉማራ፤ የወረታ ከተማም ትናንት ጀምሮ የቤት ውስጥ አድማ ላይ ናት፡፡ ትናንት ቅጥረኛ የሆኑ ሥጋ ቤታቸውን የከፈቱ 2 ግለሰቦች የወረታ ዐማሮች አዘግተዋል፡፡ መከላከያ ሠራዊት አስለቃሽ ጪስ በመጠቀም ወጣቱን የበተነ ቢሆንም መንገዶችን ሙሉበሙሉ በ መዝጋት የገባውን መከላከያ እንዳይወጣ አስጨንቀውት ሰንብተዋል፡፡ ትናንት ለዛሬ ሌሊት ጉማራ ላይ በገበሬውና በወያኔ መከላከያ መካከል ከፍተኛ ተኩስ አድሯል፡፡ በተኩስ ልውውጡ ሦስት የፎገራ ዐማሮች የተሰው ሲሆን ከሦስት በላይ የመከላከያሠራዊት አባላት ተገድለዋል፡፡ጉማራ ድልድይ መንገድ ተዘግቷል፡፡ ደባርቅ/ ጃናሞራ፤ ከደባርቅ ከተማ እስከ ጃናሞራና ደረስጌ ያለው አካባቢ ሙሉ በሙሉ ከመንግሥ ት ቁጥጥር ውጭ መሆኑን ዛሬ ሰምተናል፡፡ የፖርክ ጠበቂ የነበሩ ሚሊሻዎችን በማባረር ዐማራው ራሱን በራሱ እያስተዳደረ ነው፡፡ በለሳ/ አርባያ፤ የአርባያ በለሳ ሕዝብ መንግሥትን ካባረረ ዛሬ ሦስተኛ ቀኑ ነው፤ ሆኖም በስልክ ችግር ምክንያት የተሟላ መረጃ ማቅረብ አልቻልንም፡፡ በየቦታው መረጃ በማቅረብ ለምትተባበሩን ቁርጥ የዐማራ ልጆች ሁሉ በዐማራ ሕዝብ ስም ምስጋ ናችን ከፍ ያለ ነው፡

No comments:

Post a Comment